Showing posts with label ኪነ ጥበብ. Show all posts
Showing posts with label ኪነ ጥበብ. Show all posts

Monday, July 9, 2018

“የጋሽ ጸጋዬ ግጥሞች ቅኝት”






ከነቢይ መኮንን
.
.
እውነት ለመናገር ስለ ስነግጥም ከመናገር መግጠም ይሻላል። በተለይ እንደ ጋሽ ጸጋዬ ገብረ መድኅን ያለውን የግጥም ነዶው ተከምሮ የማያልቅ ገጣሚን ሥራ መናገር “ሂማሊያን በሁለት ቆራጣ እግር-አሊያም አባይን በጭልፋ” እንደማለት ያለ ነገር ነው። ራሱ ጋሽ ጸጋዬ እንደሚለውም “አንድ ምእመን የሃይማኖቱን ድንጋጌ ከማተቱ ይልቅ፤ በቀጥታ እግዚአብሔርን በእምነት ማገልገሉ እንደሚበልጥበት ሁሉ፤ ባለቅኔም የሥነ-ግጥሞችን የአደራደር ሥርዓትና ድንጋጌ (Form) ከማተቱ ይልቅ ቅኔውን ተቀኝቶ፣ ደርሶ፣ ፍሬ-ሃሳቡን (Content) ማበርከቱ ይበልጥበታል።”