Tuesday, July 24, 2018

የኢትዮጵያ ዘመናዊ ሕክምና ከየት እስከ የት



በባህላዊ የሕክምና ጥበብ ድልድይ ተሻግሮ ለተዓምር የቀረቡ ፈውሶችን መስጠት የቻለው ዘመናዊ ሕክምና ወደ ኢትዮጵያ የገባው ቆይቶ ነበር፡፡ ጉንፋን ሲይዘው ዳማከሴ ጨምቆ፣ አላስቆም አላስቀምጥ ለሚለው ጥርሱ ስራስር ነክሶ፣ ለሚያዋክበው ቁርጠት ጤና አዳም ጨምቆ፣ ክፉ መንፈስ ተጠናወተኝ ሲል በየሃይማኖቱ ፀልዮ፣ ድኝ ታጥኖ ሌላም ድንገተኛና አጣዳፊ ሕመም ሲያጋጥመው ቅጠል መበጠስ ለሚቀናው የኅብረተሰብ ዘመናዊ ሕክምና ብዙም አንገብጋቢ ጉዳይም አልነበረም፡፡

የቁንጅና ሚዛን


ቁንጅና እንደየማኅበረሰቡ ባህልና እሴት ሲያልፍም እንደ ዘመኑ የአስተሳሰብ ደረጃ ትርጉሙ ይለያያል፡፡ በአንድ ወቅት የቁንጅና ተምሳሌት የነበሩ ነገሮች ዘመን ሲለወጥ ትርጉማቸውም አብሮ ሲለወጥ ይስተዋላል፡፡ በየዘመናቱ በነበረው የሥልጣኔ ደረጃ የቁንጅና አረዳድ ሁኔታ ሰዎች ውብ ሆኖ ለመታየት ብዙ ነገሮችን ያደርጉም ነበር፡፡

Monday, July 23, 2018

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ የወዳጅነት ጨዋታ ሊያደርጉ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከኤርትራ አቻው ጋር በነሐሴ ወር አጋማሽ አስመራ ላይ የወዳጅነት ጨዋታ ሊያደርግ ነው።የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሁለቱን ሀገራት ወንድማማችነት ለማጠናከር አስመራ ከተማ ላይ የወዳጅነት ጨዋታ ለማድረግ ባሳለፍነው ሳምንት ደብዳቤ መላኩ ይታወሳል።

በ50 የዓለማችን አገራት የኤችአይቪ ስርጭት ጨምሯል


50 የተለያዩ የዓለማችን አገራት የኤችአይቪ ኤድስ ስርጭት እየጨመረ መምጣቱንና በቫይረሱ እየተጠቁ ካሉት ሰዎች ግማሽ ያህሉ የመድሃኒትና የህክምና አገልግሎቶችን እያገኙ እንዳልሆነ ዩኤንኤድስ የተባለው አለማቀፍ ተቋም ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡

ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የቅጅ መብት ሕግ ጥሷል ተብሎ የፍትሐ ብሔር ቅጣት ተወሰነበት


ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የቅጅና ተዛማጅ መብቶች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 410/96 እና የተሻሻለውን አዋጀ ቁጥር 872/2007 አንቀጽ (41) ተላልፏል ተብሎ፣ የተመሠረተበትን የፍትሐ ብሔር ክስ ማስተባበል ባለመቻሉ ቅጣት ተወሰነበት፡፡

Sunday, July 22, 2018

570 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በህገ-ወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጅጋ ሲጓጓዝ ተያዘ


570 ሺህ የአሜሪካ ዶላር በህገ-ወጥ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጅጋ ሲጓጓዝ በቁጥጥር ስር መዋሉን የምስራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ አስታወቀ።

ባለፉት ቀናት በተከናወነ ኦፕሬሽን 10 ሚሊየን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ መያዙን ፖሊስ ገለፀ

ጥናትን መሰረት በማድረግ ባለፉት ጥቂት ቀናት በአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ውጪ በተከናወነ ኦፕሬሽን በህገወጥ መንገድ የተያዘ 10 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ መያዙን የፌደራል ፖሊስ ገለፀ።